የምድር ሳይሆን የህዝብ ንጉስ
2 ኛ ሳሙኤል 5
******************************
በዘዳግም መጽሐፍ (17 :15) ውስጥ ንጉሥ እንዴት መሾም እንደሚቻል የሚያሳይ መመሪያ እናያለን ፡፡ ትክክለኛውን እጩ በመምረጥ በአምላክ ላይ ብቻ የሚመረኮዘው ህዝብ ነው ፡፡ ለዚህም ነው ንጉሱ የህዝብ እንጂ የመሬቱ ንጉስ ያልሆነው። በተለይ በአለም ላይ ያሉ ንጉሶችንና አነጋገሳቸውን ስናይ ሁሉም መሬቱን በግላቸው በማዋል ለላው ህብረተሰብ የንጉሶቹ ጭሸኛ እንደሆነ መለስ ቀለስ ብለን የምናነባቸው የታሪክ መጣጥፎች ይነግሩናል።ይህ እንደሚያመለክተው ከዳዊት በላይ ብቸኛው ንጉስ ወይም የግኡዙ ፍጥረት ባለቤት የሆነው ፣ እግዚአብሔር እንደሆነና ዳዊት ግን ህዝቡን የማስተዳደር ውክልና እንዳለው የሚያመለክት ህገ መንግስት ነው፡፡
ይህ ሃሳብ ዛሬ በምናነበው የ II ሳሙኤል ምእራፍ ላይ እናያለን።ጠልቀን ማንበብ ብንችል ከመጀመሪያውም ዳዊትልንገስ ብሎ ሳይሆን ከ ካህኑ ሳሙኤል ምርጫ ጀምሮ ዳዊት ለንጉስነት እንደታጨ እናያለን። በዚህ ምእራፍ ላይም ዳዊት ኬብሮን በነበረበት ሰአት የእስራኤል ነገዶች ወደ ኬብሮን በመምጣት ዳዊት መጥተው ለእርሱ ታማኝ መሆናቸውን ሲያውጁ እናያለን። ይህም የሚያመለክተው የምርጫው ውጤት እንደሚያመለክተው ዳዊት በአብዛኛው ወንበር ማሸነፉን ይገልጽልናል። እነሱ ዳዊት ንጉሥ እንዲሆን የእግዚአብሔርን ፍላጎት ይቀበላሉ ፣ ከዚያ ሽማግሌዎች ቃልኪዳን አድርገው ዳዊትን የእስራኤል ንጉሥ እንዲሆን ቀቡት፡፡ እንግዲህ ይህ የሚያመለክተን ዳዊት ንጉስ ለመሆን በራሱ አላወጀም ግን የህዝቡን ውሳኔ ተቀበለ እንጂ።ለንጽጽር ይሆን ዘንድ ራሳቸውን ንጉስ ለማድረግ በሃብታቸው በጦር ሃይላቸው የሚመኩበአለማችን ያሉ የኖሩ ብዙ ነገስታት አሉ።
ይህ ዳዊት የሚያልፈው ሦስተኛው ቅባት ነው - በመጀመሪያ በሳሙኤል (1 ኛ ሳሙኤል 1 ፣ ምዕራፍ 16) ከዚያም በይሁዳ (ሳሙኤል II ፣ ምዕራፍ 2) እና አሁን እዚህ በመላው እስራኤል ፡፡ እያንዳንዱ ቅብዓት የዳዊትን ኃይል ያሰፋዋል ፣ በመጀመሪያ እሱ በእግዚአብሔር መመሪያ የተቀባ ነው ፣ ከዚያ የያዕቆብን በረከት ለአባቱ ቅድመ አያት ይሁዳ ያመጣለታል ፣ ይህም የእሱ ዘሮች ከመካከላቸው አንድ ንጉሥ ይሾማሉ ፣ ከዚያ ደግሞ በመላው እስራኤል ሕዝብ።
በአንዳንድ መንገዶች እነዚህ ቅባቶች ከዳዊት ሕይወት ጋር እንደሚዛመዱ እንመለከታለን ፡፡ እረኛ፣ ተዋጊ.እና መሪ ፡፡ እረኛው መንጋውን በመንከባከብ በብቸኝነት ይንከራተታል ነገር ግን ብዙ ጊዜ ሳይስተዋል ይቀራል ፡፡ ሙሴም እረኛ ነበር ፣ እንደ ዳዊትም ሁሉ የመንጋውን ጉዞ እየተከተለ ያለው እግዚአብሔር ብቻ ነበር ፡፡ ሙሴ በእረኛ ተግባሩ በመለኮታዊነት የተሾመ ሲሆን ዳዊትም እንዲሁ ፡፡
ከዚያም ዳዊት እንደ ጦር ተዋጊ ፣ የጦር ሜዳ አዛዥ ሆነ ፡፡ አንድን አጠቃላይ ህዝብ በዙሪያው የማሰባሰብ አቅም ገና የለውም ፡፡ ልክ እንደ ተዋጊ ፣ እሱ ቅርብ ለሆኑት ሰዎች አክብሮት ያዝዛል ፣ ስለሆነም በእነሱ ላይ ለመምራት ከፍ ያለ በጎሳ የትዳር አጋሮች መቀባቱ ምክንያታዊ ነው።
በመጨረሻም ፣ እሱ ተዋጊ ከመሆን ወደ መሪነት ይሸጋገራል። እሱ የእስራኤልን ህዝብ ሁሉ ወደሚያካትት ራዕይ ፣ የትግል ሜዳ ልምዱን ማለፍ ይችላል; እሱ ግልጽ ፣ ባለራዕይ እና አንድ አገርን ነው የሚወክለው። ስለዚህ በመጨረሻ በሁሉም የአገሪቱ ሽማግሌዎች ተቀባ ፡፡
እሱ መለኮታዊ ሃላፊነት ያለበት ንጉስ ነው ፡፡ የዳዊት ድርጊቱ በሕዝብ ዘንድ እንዲወደድ አድርጎታል ፣ እናም ይህን ሲያደርግ የእስራኤል ምድር ንጉሥ ሳይሆን ፣ የእስራኤል ሕዝብ ንጉሥ ነው ፣ በዘመናት ሁሉ የሚዘመር ቀጣይነት ያለው ንግሥና ሳይሆን በህዝብ ምርጫ የሚቀየር ንጉስ። ግን ለምን 40 ዓመት ምክንያቱም ሙሉ የስልጣን ጊዜ ስለነበር። ሳኦል ሙሉ የስልጣን ዘመኑን ሳይጨርስ ሞቷል።
ምርጫ ምን ያህል ለመረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ያለንበት ክፍለ አህጉር ምን ያህል በምርጫ መጭበርበር እየታመሰች መረዳት አንድ መንገድ ነው። ምንም በአፍሪካዊነት ባምንም ይህንን ህልም ተግባራዊ ለማድረግ የሚደረገው ማጭበርበር የምናውቀው የአህጉራችን እውነታ ነው። የአፍሪካ አባት
የተሰኙት የጋናው ክዋሜ ንክሩማህ የተመራውው የካዛብላንካ ህብረት የሁሉም የአፍሪካ አገራት ፌዴሬሽንን የማቋቋም ህሳቤ ይዞ የተነሳ ድንቅ ሃሳብ ቢሆንም የዚሁ ሃሳብ አመንጪ የተከበሩት ከዋሜ ባገራቸው ላይ ምን ያህል ጥላቻ እንደነበረባቸው የአፍሪካ ታሪክ መጽሃፍቶቻችን ቁልጭ አድርገው የጻፉት ሃቅነው። በእውነቱ ክዋሜ ሚስታቸው ከግብጽ እንድትሆን የፈለጉበት አላማም ይህንኑ የሳቸው ሃሳብ የሆነውን ፌዴሬሽን ለመፍጠር ይመስላል። ግን የሳቸው ሃሳብ በአገራቸው እንኳን አልተገበረም። በሙስና በግፍ የሳቸው ታሪክ ከጋና እስከመባረር እንዳደረሳቸው እናነባለን። ከዚህ ንጽጽር አኳያ እስራኤልን አንድ ለማድረግ ዳዊት የሄደበት ሁኔታ ጥያቄ ውስጥ ሊገባ ይችላል። ለምሳሌ የዋና ከተማውን ከሄብሮን አንስቶ ጀሩሳሌም ያደረገው በግልጽ እንደተጻፈው ያአያቶቹን ስምምነት እንኳን በማፍረስ ነው። የኢያቡሳውያን ከተማ የሆነችውን እየሩሳሌምን በግድ ወስዷል። ይህ ሁሉ ለአንድነት ሲባል የሚከፈለው ዋጋ ነው። ባጣም የራቀ ታሪክ እንደ ዳዊት እና የአህጉራችን ውጣውረድ ምን ይነግረናል? ይህ ጥናት ሃይል ወዳቂ ምርጫ ዘላቂ መሆኑን አስተምሮኛል። የዘመናት ታሪክ የሚነግሩን ሌላውን መግዛት በፍጹም የማይቻል መሆኑን ላንዴ እንኳን ብንገነዘብ ሰላም የተሞላበት ህይወት ይኖረናል።ሻሎም!

አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ